የብሪክስ ሳይንቲስቶች በውቅያኖስ እና በዋልታ ምርምር ዙሪያ በሩሲያ ሙርማንስክ ከተማ በጋራ እየተወያዩ ነው።
"እ.ኤ.አ በ 2024 ሩሲያ የብሪክስ ሊቀመንበርነት መሆኗን ተከትሎ፤ ሙርማንስክ ከ ሰኔ 13 እስከ 15 ለሚካሄደው በውቅያኖስ እና በዋልታ ሳይንስ (polar science ) እና ቴክኖሎጂ ዙሪያ ለስድስተኛ ጊዜ የሚደረገው ለማስተናገድ ተመርጣለች" ሲሉ የክልሉ የመረጃ እና ፖሊሲ ሃላፊ ተናግረዋል።
የብሪክስ ሀገራት በውቅያኖስ እና ዋልታ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ልማት ላይ ንቁ ተሳትፎ ያደርጋሉ።
የስራ ቡድኑ ተልእኮ ፤ በብሪክስ አባል ሀገራት መካከል በውቅያኖስ ሳይንስ እና በዋልታ ምርምር ላይ መንግስታትን፣ ዩኒቨርሲቲዎችን፣ የምርምር ተቋማትን እና ኢንዱስትሪዎች ያቀፈ የጋራ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ በመካከላ ቸው ያለውን ትብብርን ማሳደግ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia