ሰኔ 12 ቀን የተከበረውን የሩሲያ ቀን ምክንያት በማድረግ ኒጄሪያዊቷ ልጃገረድ የሩሲያ ብሄራዊ መዝሙር ዘምራለች
በኒያሚ በሚገኘው በሩስያ ሃውስ (ባህል ማዕከል) ውስጥ በተሰናዳው ዝግጅት ላይ ብሄራዊ መዝሙሩን የዘመረችው ሳዉዳቴ መሀመድ ከእንግዶቹ ዘንድ ከፍተኛ ጭብጨባ እንደተቸራት የስፑትኒክ ዘጋቢ ገልጿል።
ልጅቷ የሩሲያ ባንዲራ ቀለም ያለውን ልብስ ፤ እንዲሁም የኒጄር ባንዲራ ቀለም ያለው ኮፍያ አድርጋ ነበር።
በትላንትናው እለት በኒጀር ዋና ከተማ የሩስያ ባህል ማዕከል ተከፍቷል። የባህል ማእከሉ ዳይሬክተር ቤሎ ኢሱፉ አህመድ ለስፑትኒክ እንደተናገሩት “የባህል ማዕከሉ መከፈት በኒጀር እና በሩሲያ መካከል ያለው ግንኙነት እየተሻሻለ መምጣቱን ያሳያል ብለዋል።
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንደገለጸው ሩሲያ በኒጀር ኤምባሲዋን በመክፈት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማሳደግ እየሰራች ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia