የናይጄሪያው ፕሬዝዳንት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን ለማድረግ ቃል ገብተዋል፤ ዝቅተኛ የደመወዝ ክፍያ መነሻ ወለል ረቂቅ አዋጅ አስተዋውቀዋል።
የናይጄሪያው ፕሬዝዳንት ቦላ ቲኒቡ እሮብ እለት እንዳሉት ፤በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን የኢኮኖሚ ችግሮች እንደሚረዱና የኢኮኖሚ ማሻሻያ በማድረግ የናይጄሪያውያን ዜጎችን ህይወት ለማሻሻል እና የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን ቃል ገብተዋል።
"ኢኮኖሚያችን ለአስር ዓመታት የሚፈጅ ማሻሻያዎችን ይፈልጋል፤ ሚዛናዊ ያልሆነ እና በነዳጅ ዘይት በሚገኝ ገቢ ላይ ከመጠን በላይ ጥገኛ የሆነ ኢኮኖሚ ነው "ሲሉ በቴሌቭዥን በተላለፈ መልእክታቸው ተናግረዋል።
ህዝባዊ አመፅን የቀሰቀሱ ችግሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ ቢሄዱም የኢኮኖሚ ማሻሻያዎቹ እንደሚቀጥሉ እና አዲስ ዝቅተኛ የደመወዝ ክፍያ ወለልን፤ በቅርቡ ለብሔራዊ ምክር ቤት አቅርበው በስራ አስፈፃሚ አቅርበው እንደሚያጸድቁ አስረድተዋል።
“ ከሠራተኛ ማህበራት አመራሮች ጋር በጥሩ መንፈስና በቅን ልቦና፤ አዲሱን ዝቅተኛ የደመወዝ ክፍያ መነሻ ወለል ላይ ተወያይተናል። ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ወይም ከዚያ ባነሰ ጊዜ ውስጥ የህጋችን አካል ሆኖ እንዲፀድቅ በቅርቡ ወደ ብሄራዊ ምክር ቤት እንልካለን ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia