የፈረንሳይ ማዕድን አውጪ ኩባንያ ኦራኖ አዲስ የዩራኒየም ማዕድን ቁፋሮ በኒጀር ሊጀምር እንደሆነ ተዘገበ።
የኦራኖ ኩባንያ እህት ኩባንያ አካል የሆነው "ኢሞራረን ኤስ ኤ ፤በኢሞራረን ማዕድን ማውጫ ያለውን ዩራኒየም ለማምረት የመጀመሪያው የዝግጅት ምዕራፍ ላይ ደርሷል፤ "በቅርብ ጊዜ ውስጥ ሥራዎችን ይጀምራል" ማለታቸውን የኩባንያውን ቃል አቀባይ በመጥቀስ ኤ.ኤፍ .ፒ ዘግቧል።
አሞራረን በኒጀር ሰሜናዊ ምዕራብ ፤በአርሊት ክልል የሚገኝ የዩራኒየም ክምችት የሚገኝበት አካባቢ ሲሆን፤በአሁኑ ጊዜ ኦራኖ በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል የሚገኘው የሶማይር ማዕድን ማውጫን ያስተዳድራል።
እ.ኤ.አ በ 2021 ሁለተኛው የኮሚናክ ማዕድን በኬሚካል እጥረት ምክንያት ከአገልግሎት ውጭ ሆኗል ፣ እ.አ.አ በ 2024 መጀመሪያ ላይ ምርት ለማስጀመር ተይዞ የነበረውም እቅድ ለሌላ ጊዜ መተላለፉ ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia