ሩሲያ ቤላሩስ የብሪክስ ህብረትን ለመቀላቀል የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ተናገሩ።
"ቤላሩስ ብሪስስን ለመቀላቀል ያስገባቸውን ማመልከቻ ተቀባይነት እንዲያገኝ ድጋፋችንን እንሰጣለንን" ሲሉ የሩሲያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ሪያብኮቭ ማክሰኞ ከቤላሩስ ብሮድካስቲንግ ( ሲቲቢ) ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል ።
ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አክለውም ቤላሩስ " ብሪክስ በሚሰራባቸው ሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ማለትም በፖለቲካ እና ደህንነት፣ በኢኮኖሚ እና ፋይናንስ፣ በሰብአዊ ጉዳዮች እንዲሁም በህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እና ባህል ዙሪያ ጠንካራ ሀገር ነች ብለዋል።"
ቤላሩስ ባለፈው ዓመት ብሪክስን ለመቀላቀል አመልክታለች። የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ አሌኒኒክ ሚንስክ በጥቅምት ወር በሩሲያ ካዛን በሚካሄደው የድርጅቱ ጉባኤ በ ብሪክስ ውስጥ በአዲስ ደረጃ ለመድረስ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia