የሰኔ 3 የምሽት ዋና ዋና የዓለም ጉዳዮች፦
🟠 የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናሌዲ ፓንዶር ለስፑትኒክ አፍሪካ ልዩ ቃለ ምልልስ ሰጥተዋል።
🟠 ናሌዲ ፓንዶር እና የሩስያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ደቡብ አፍሪካ እና ለሌሎች የደቡባዊ ዓለም ሀገራት በዩክሬን ግጭት አፈታት ዙርያ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ የሚያደርጉበትን መንገድ ተወያይተዋል።
🟠 የ "ሩስያ-24" የቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኛን ጨምሮ አራት ሰዎች በሩስያ ቤልጎሮድ ክልል ውስጥ በፈነዳ ፈንጂ እንደሞቱ የክልሉ አስተዳዳሪ ገለፁ።
🟠 ቻይና በብሪክስ ውስጥ ስትራቴጂካዊ አጋርነቷን ለማጠናከር ከሩስያ ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆኗን እና በድርጅቱ የሩስያን ሊቀመንበርነት እንደምትደግፍ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከላቭሮቭ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስታውቀዋል።
🟠 እስራኤል ከሃማስ ጋር የምታደርገው ድርድር ካልተሳካ አምስት አሜሪካውያን ታጋቾችን ለማስፈታት ዩናይትድ ስቴትስ ከቡድኑ ጋር የአንድ ወገን ስምምነት ልትፈፅም እንደምትችል የምእራባውያን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
🟠 ዩናይትድ ስቴትስ እና ፖላንድ በመረጃ ዙርያ ሩስያን የሚመክት እና ዩክሬንን የሚደግፍ ቡድን እያቋቋሙ እንደሆነ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት የፕሬስ አገልግሎት አስታወቀ።
🟠 በደቡባዊ ፖላንድ የሮኬት ነዳጅ በሚመረትበት "መስኮ" የጦር መሳሪያ ፋብሪካ ከባድ ፍንዳታ ደረሰ።
🟠 ሩስያ በልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽን ስፍራ "ጎሉብ" የተባለ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ሰርታ በተሳካ ሁኔታ መሞከሯን ድሮኑን ያበለፀገው ድርጅት ተወካይ ገልፀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia