ፈረንሳይ የዩክሬን ወታደሮችን በፍፁም በቀጥታ አሰልጥና አታውቅም፤ አሰልጣኞችን መላክ ግን ክልክል አይደለም ፤ ሲሉ የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ።
ቀደም ሲል ቫሉርየስ አኩሊየስ የተሰኘው መገናኛ ብዙሃን፤ ጡረታ የወጡ የፈረንሳይ የባህር ሃይል ኮሎኔል ፔር ዴ ጆንግን በመጥቀስ የፈረንሳይ ጦር ቀድሞውንም ቢሆን በዩክሬን ፤የጦር መሳሪያዎችን በመጠገን እና በማሰልጠን ላይ እንደሚገኝ ዘግቦ ነበር።
ሩሲያ ወደ ለዩክሬን የሚቀረበውን የጦር መሳሪያ ድጋፍ እንደ ቀጥተኛ ድጋፍ እንደምትቆጥው፤ የኔቶ ሀገራትን ደጋግማ አስጠንቅቃለች። ሞስኮ የኔቶ ሀገራት ዩክሬንን ማስታጠቃቸው "በእሳት መጫወት ነው" ያለች ሲሆን፤ ይህን መሰል ድርጊቶች የሩስያ እና ዩክሬን ሊኖር ለሚችለው የሰላም ድርድር እንቅፋት መሆኑን ገልጻለች።
ለኪየቭ አገዛዝ የረጅም ርቀት የጦር መሳሪያዎች ማቅረቡ ፤ወደ ከፋ ችግር ውስጥ ሊወስድ እንደሚችል፤ ቭላድሚር ፑቲን በትላንትናው እለት ከዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ወኪሎች ጋር ባደረጉት ስብሰባ ላይ አስጠንቅቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia