የግንቦት 27 ረፋድ ዋና ዋና የአለም ዜናዎች
🟠 ፍልስጤም የዘር ማጥፋት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቅጣት የወጣውን ስምምነት በመተላለፍ ፤ ደቡብ አፍሪካ በእስራኤል ላይ ያቀረበችውን ክስ በመቀላቀል ፤ለአለም አቀፉ ፍርድ ቤት አቤቱታ አቀረበች።
🟠 የናይጄሪያ መንግስት እና የሀገሪቱ የሠራተኞች ህብረት ስምምነት ተፈራረመው። ፕሬዝዳንቱ የሀገሪቱ ዝቅተኛ ደሞዝ ወለል ከ60,000 ኒያራ (40 ዶላር) በላይ እንዲሆን ቃል ከገቡ በኋላ ነው ስምምነት ላይ የተደረሰው። በሀገር አቀፍ ደረጃ በተጠራው የሥራ ማቆም አድማ ወቅት ሀገሪቱ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ አጋጥሟታል።
🟠 በአህጉሪቱ እየተከሰቱ ያሉ ግጭቶች ለማስቆም ሠላምና መረጋጋት ለማስፈን ፤ የአፍሪካ ተጠባባቂ ሃይል እንዲኖር፤ እንዲሁም የተቀናጀ ጥረት እንዲደረግ የአፍሪካ ህብረት አሳሰበ።
🟠 የሩስያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ኮንጎ ሪፐብሊክ መግባታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ ተናግረዋል።
🟠 የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴር የ"እንቁራሪት"መሰል ሮቦት በአውደ በውጊያ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ ማዋሉን ተናግሯል። በእንቁራሪት"መሰል ሮቦት በአቭዴዬቭካ አካባቢ አንድ የዩክሬን የጦር መሳሪያ አውድሟል።
🟠 የኔቶ ዋና ጸሃፊ ስቶልተንበርግ ሩሲያ የመከላከያ ኢንዱስትሪዋን ከተጠበቀው በላይ ማጠናከሯን አምነው ፤ የጦር መሳሪያ ምርትን አሳድገዋል ሲሉ ግን፤ የኔቶ ሀገራት ላይ ቅሬታ ያሰማሉ ብለዋል።
🟠 የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ፓርቲ ጥምረት በህንድ ፓርላማ ምርጫ አብላጫውን መቀመጫ አገኘ ፤ይፋ በሆነው የምርጫ ውጤት መሰረት ከ85 በመቶ በላይ ድምጽ አግኝቷል።
🟠 የፓፑዋ ኒው ጊኒ ባለስልጣናት በቅርቡ የተፈጥሮ አደጋ በተከሰተበት ቦታ ላይ ፤አዲስ የመሬት መንሸራተት አደጋ ሊያጋጥም እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia