የግንቦት 26 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች
🟠 የሩስያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ በጊኒ ሪፐብሊክን ጉብኝታቸው ወቅት ከጊኒ አቻቸው ሞሪሳንዳ ኩያቴ ጋር ተወያይተዋል።
🟠 ክላውዲያ ሺንባም የሜክሲኮ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫን በማሸነፋቸው ቭላድሚር ፑቲን የእንኳን ደስ ያሎት መልእክታቸውን ማስተላለፋቸውን ክሬምሊን አስታውቋል።
🟠 የሩስያ ፌዴራል የጸጥታ አገልግሎት ፤ በሩሲያ መሰረተ ልማቶች እና በወታደራዊ መኮንኖች ላይ በማሴር ጉዳት ለማድረስ በሴባስቶፖል ግዛት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የዩክሬን የስለላ ወኪሎች መረብ ማግኘቱን ኤጀንሲው አስታውቋል።
🟠 ኔታንያሁ ታጋቾችን ለማስለቀቅ በጋዛ የሚካሄደውን ወታደራዊ እርምጃ ለ42 ቀናት ለማቆም ፍቃደኛ መሆናቸውን አስታውቀዋል፤ ነገርግን ሁሉም አላማዎች እስኪሳኩ ድረስ ጦርነቱን ማቆም እንደማይችሉ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
🟠 የኢራን ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት መሀመድ ሞክበር በመጪው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በእጩነት አይመዘገቡም።
🟠 የሩስያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ፅህፈት ቤት በኖርድ ስትሪም የነዳጅ ማስተላለፊያ ላይ የተፈፀመውን የአሸባሪዎች ጥቃት አስመልክቶ ለአሜሪካ፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይ እና ቆጵሮስ ተጨማሪ ጥያቄዎችን ልኳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia