አብዛኛዎቹ የሪፐብሊካን መራጮች በትራምፕ የጥፋተኛነት ውሳኔ ሀሳባቸውን አልለወጡም፤ አንዳንዶች ድጋፋቸውን እየጨመሩ እንደሆነ የሕዝብ አስተያየት መስጫ አሳየ።

አብዛኛዎቹ የሪፐብሊካን መራጮች በትራምፕ የጥፋተኛነት ውሳኔ ሀሳባቸውን አልለወጡም፤ አንዳንዶች ድጋፋቸውን እየጨመሩ እንደሆነ የሕዝብ አስተያየት መስጫ አሳየ። የኒውዮርክ ዳኞች፤ የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ የንግድ መዝገቦችን በማጭበርበር ጥፋተኛ ብለው በወሰኑት ውሳኔ፤ አብዛኞቹ የዩናይትድ ስቴትስ ሪፐብሊካን መራጮች ድምፃቸውን አንደማይቀይሩ፤ አርብ እለት ይፋ የሆነው የሮይተርስ/አይፒኤስኦኤስ (Ipsos) የሕዝብ አስተያየት መስጫ አመላክቷል። አብዛኞቹ የሪፐብሊካን አስተያየት ሰጭዎች (56%) በቅጣት ውሳኔው መሰረት ድምፃቸውን እንደማይቀይሩ፣ ከአንድ ሶስተኛ በላይ (35%) ትራምፕን መደገፋቸው እንደማይቀር እና 10% ብቻ ለትራምፕ ላይመርጡ እንደሚችሉ የህዝብ አስተያየቱ አመልክቷል። በተመሳሳይ፤ 56% የሚሆኑት ገለልተኛ አስተያየት ሰጪዎች የምርጫ ውሳኔያቸውን እንደማይለውጡ፣ 25% ያህሉ ለትራምፕ ላይመርጡ እንደሚችሉ እና 18% ደግሞ ከጥፋተኝነት ውሳኔው በኋላ ለትራምፕ መምረጣቸው የሚጠበቅ እንደሆነ፤ የህዝብ አስተያየት መረጃው አሳይቷል። ሐሙስ እለት ዶናልድ ትራም ለወሲብ ፊልም ተዋናይት ስቶርሚ ዳንኤልስ በድብቅ የከፈሉትን ገንዘብ ለመሸፈን፤ የንግድ መዝገቦች እጭበርብረዋል በተባሉበት 34 ክሶች ጥፋተኛ ተብለዋል። ትራምፕ የቀረበባቸውን ውንጀላ ውድቅ አድርገው፤ ይግባኝ እንደሚሉ ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
አብዛኛዎቹ የሪፐብሊካን መራጮች በትራምፕ የጥፋተኛነት ውሳኔ ሀሳባቸውን አልለወጡም፤ አንዳንዶች ድጋፋቸውን እየጨመሩ እንደሆነ የሕዝብ አስተያየት መስጫ አሳየ። የኒውዮርክ ዳኞች፤ የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ የንግድ መዝገቦችን በማጭበርበር ጥፋተኛ ብለው በወሰኑት ውሳኔ፤ አብዛኞቹ የዩናይትድ ስቴትስ ሪፐብሊካን መራጮች ድምፃቸውን አንደማይቀይሩ፤ አርብ እለት ይፋ የሆነው የሮይተርስ/አይፒኤስኦኤስ (Ipsos) የሕዝብ አስተያየት መስጫ አመላክቷል። አብዛኞቹ የሪፐብሊካን አስተያየት ሰጭዎች (56%) በቅጣት ውሳኔው መሰረት ድምፃቸውን እንደማይቀይሩ፣ ከአንድ ሶስተኛ በላይ (35%) ትራምፕን መደገፋቸው እንደማይቀር እና 10% ብቻ ለትራምፕ ላይመርጡ እንደሚችሉ የህዝብ አስተያየቱ አመልክቷል። በተመሳሳይ፤ 56% የሚሆኑት ገለልተኛ አስተያየት ሰጪዎች የምርጫ ውሳኔያቸውን እንደማይለውጡ፣ 25% ያህሉ ለትራምፕ ላይመርጡ እንደሚችሉ እና 18% ደግሞ ከጥፋተኝነት ውሳኔው በኋላ ለትራምፕ መምረጣቸው የሚጠበቅ እንደሆነ፤ የህዝብ አስተያየት መረጃው አሳይቷል። ሐሙስ እለት ዶናልድ ትራም ለወሲብ ፊልም ተዋናይት ስቶርሚ ዳንኤልስ በድብቅ የከፈሉትን ገንዘብ ለመሸፈን፤ የንግድ መዝገቦች እጭበርብረዋል በተባሉበት 34 ክሶች ጥፋተኛ ተብለዋል። ትራምፕ የቀረበባቸውን ውንጀላ ውድቅ አድርገው፤ ይግባኝ እንደሚሉ ተናግረዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia