የሩሲያ-ታንዛኒያ የክትባት ማምረቻ ፕሮጀክት የታንዛኒያን የጤና ሉዓላዊነት ሊያሳድግ ይችላል - ኬንያዊ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

የሩሲያ-ታንዛኒያ የክትባት ማምረቻ ፕሮጀክት የታንዛኒያን የጤና ሉዓላዊነት ሊያሳድግ ይችላል - ኬንያዊ ባለሙያ

​የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚያደርጉ እና የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎችን የሚገነቡ ኢንቨስትመንቶች ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ በመሆናቸው፤ የታንዛኒያ የመድኃኒት ዘርፍ ከሩሲያ ጋር ከሚደረገው አጋርነት "ትልቁ ተጠቃሚ" ሊሆን ይችላል ሲሉ የመንግሥት አስተዳደር እና ኢኮኖሚ ባለሙያው ፍሬድሪክ ኦንያንጎ ኦጎላ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ባለሙያው ሲያብራሩም "[የሀገር ውስጥ የክትባት ምርት] ከውጭ በሚገቡ ክትባቶች ላይ ያለውን ጥገኝነት የሚቀንስ እና የአፍሪካን የመድኃኒት ነጻነት የሚያጠናክር ነው። ይህ ከክትባት ተጠቃሚነት ወደ ክትባት አምራችነት መሸጋገር ማለት ነው" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በተጨማሪም የሩሲያ እና ታንዛኒያ ትብብር "እውነተኛ ውጤት" በክትባት ምርት የሀገር ውስጥ እውቀት መዳበሩ እና የእሴት ሰንሰለት ማደጉ ነው ሲሉ ኦጎላ አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0