ኤም23 አማፂያን የምስራቅ ኮንጎ የሰላም ጥረቶችን ለማገዝ ከያዙት ዋሊካሌ ከተማ እንደሚወጡ አስታወቁ

ሰብስክራይብ
ኤም23 አማፂያን የምስራቅ ኮንጎ የሰላም ጥረቶችን ለማገዝ ከያዙት ዋሊካሌ ከተማ እንደሚወጡ አስታወቁ ኤም23ን የሚያካትተው የኮንጎ ወንዝ ህብረት የካቲት ውስጥ በተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት እንደሚገዛ እና ሰላምን እንደሚደግፍ ገልጿል። በተጨማሪም ከዋሊካሌ እና በዚህ ሳምንት በአቅራቢያው ከያዛቸው አካባቢዎች “ወታደራዊ ኃይሉን እንደሚያስወጣ” አስታውቋል። የዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ መንግሥት የኤም23 የመውጣት ውሳኔ፤ ቡድኑ በአውሮፓ ሕብረት ማዕቀብ ምክንያት የታቀዱ ውይይቶችን ከሰረዘ በኋላ፤ መሻሻሎችን እንደሚያመጣ ተስፋ አድርጓል። ንግግሩ ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ቺሸኬዲ ከቡድኑ ጋር ውይይት ላለማድረግ የያዙትን አቋም በመቀልበስ ከአማፂያኑ ጋር የሚያደርጉት የመጀመሪያው ቀጥተኛ ግንኙነት ይሆን ነበር። ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሩዋንዳ የታጠቁ ቡድኖችን በመላክ ሉዓላዊነቷን እና የግዛት አንድነቷን እንደጣሰች የምትከስ ሲሆን ሩዋንዳ ግን ለኤም23 ቡድን ወታደራዊ ድጋፍ እንደማትሰጥ በመግለፅ ክሱን ወድቅ ታደርጋለች። ሩዋንዳ በበኩሏ ኮንጎ ከ1994ቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ጋር ግኑኝነት ያላቸውን የሩዋንዳ ነፃ አውጪ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎችን እንደምትደግፍ ትገልጻለች።በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
አዳዲስ ዜናዎች
0