ሩሲያ የአፍሪካን የኃይል ክፍተት ለመሙላት ዝግጁ ነኝ አለች የሩሲያ ኢነርጂ ሚኒስቴር የዓለም አቀፍ ትብብር ምክትል ዳይሬክተር ዲሚትሪ ፖዱዬቭ ሀገሪቱ የኢነርጂ ሀብቶችን ለማቅረብና ቴክኖሎጂዎች እና ልምዶችን ለማጋራት ፍቃደኛ ነች ብለዋል። የሩሲያ እገዛ በአዲስ የማምረቻ መሠረተ ልማት ዙሪያ አቅም መገንባት እና ነባር መሠረተ ልማቶችን ማዘመን ላይ እንደሚያተኩር ጠቁመዋል። "ሩሲያ፣ ህንድ እና አፍሪካ፡ ያለፈው ትምህርት እና የወደፊቱ ተስፋ" በሚል ርዕስ መጋቢት 10 በሞስኮ በተካሄደው ሲምፖዚየም ላይ ንግግር ያደረጉት ፖዱዬቭ፤ የሩሲያ ድርጅቶች የአፍሪካን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት በቂ አቅም እንዳላቸው ገልፀዋል። የአፍሪካ ሀገራት በበኩላቸው በ2019 እና 2023 በተካሄዱት ሁለቱ የሩሲያ-አፍሪካ ጉባዔዎች፤ ከሩሲያ ጋር ለመተባበር ያላቸውን ቁርጠኝነት ማሳየታቸውን ፖዱዬቭ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
https://amh.sputniknews.africa
ሩሲያ የአፍሪካን የኃይል ክፍተት ለመሙላት ዝግጁ ነኝ አለች
ሩሲያ የአፍሪካን የኃይል ክፍተት ለመሙላት ዝግጁ ነኝ አለች
Sputnik አፍሪካ
ሩሲያ የአፍሪካን የኃይል ክፍተት ለመሙላት ዝግጁ ነኝ አለች የሩሲያ ኢነርጂ ሚኒስቴር የዓለም አቀፍ ትብብር ምክትል ዳይሬክተር ዲሚትሪ ፖዱዬቭ ሀገሪቱ የኢነርጂ ሀብቶችን ለማቅረብና ቴክኖሎጂዎች እና ልምዶችን ለማጋራት ፍቃደኛ ነች ብለዋል። የሩሲያ እገዛ... 23.03.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-03-23T12:02+0300
2025-03-23T12:02+0300
2025-03-23T12:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий