ኢትዮጵያ ንፁህ እና ዘላቂ ኢነርጂን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ጥረት እንደምትቀጥል አረጋገጠች

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ንፁህ እና ዘላቂ ኢነርጂን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ጥረት እንደምትቀጥል አረጋገጠች ኢትዮጵያዊ በብራዚል ዋና ከተማ ብራዚሊያ በተካሄደው የብሪክስ ከፍተኛ የኢነርጂ አመራሮች ስብሰባ ላይ ተሳትፋለች። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ በውይይቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የረዥም ጊዜ ዝቅተኛ የካርቦን ልቀትን ጨምሮ ሌሎች ሀገራዊ እቅዶችን እና ስትራቴጂዎችን እየተገበረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ንፁህ እና ዘላቂ ኢነርጂ ኃይል ለማረጋገጥ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት የሀገሪቱን የኃይል ፍላጎት ማሟላቷን እና ክልላዊ ውህደትን አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልፀዋል። በብሪክስ መድረክ በኢነርጂ ዙሪያ ምርጥ ተሞክሮዎች፣ ልምዶች እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ጅምሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ለቡድኑ አባል ሀገራት ጥሪ እንዳቀረቡ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ጠቁሟል።@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
አዳዲስ ዜናዎች
0