ደቡብ ሱዳን እና ሳዑዲ አረቢያ ኢኮኖሚያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር በሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሊድ ቢን አብዱልከሪም የተመራ የልዑካን ቡድንን በጁባ አግኝተዋል።የሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር እና የደቡብ ሱዳን ምክትል ሚኒስትር መንደይ ሰማያ ኩምባ ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት ዝርጋታ ግንኙነታቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ያላቸውን ቁርጠኝነት እና ትሥሥራቸው ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።ፕሬዝዳንት ኪር የልዑካን ቡድኑን ተቀብለው ሳዑዲ አረቢያ የደቡብ ሱዳን ቁልፍ የልማት አጋር እንደሆነች እውቅና የሰጡ ሲሆን፤ ሁለቱ ሀገራት ትብብራቸውን ለማስፋት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸውም አመላክተዋል፡፡በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
https://amh.sputniknews.africa
ደቡብ ሱዳን እና ሳዑዲ አረቢያ ኢኮኖሚያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
ደቡብ ሱዳን እና ሳዑዲ አረቢያ ኢኮኖሚያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
Sputnik አፍሪካ
ደቡብ ሱዳን እና ሳዑዲ አረቢያ ኢኮኖሚያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር በሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሊድ ቢን አብዱልከሪም የተመራ የልዑካን ቡድንን በጁባ አግኝተዋል።የሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጪ... 20.03.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-03-20T18:41+0300
2025-03-20T18:41+0300
2025-03-20T19:14+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий