“እኛ ሴቶች ማንኛውንም ነገር ማድረግ እንችላለን"፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሴት አውሮፕላን አብራሪ ሴቶች ህልማቸውን እንዲያሳኩ አበረታታች

ሰብስክራይብ
“እኛ ሴቶች ማንኛውንም ነገር ማድረግ እንችላለን"፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሴት አውሮፕላን አብራሪ ሴቶች ህልማቸውን እንዲያሳኩ አበረታታች "የመሸነፍ ሰሜት አይሰማቹ፤ ማንኛውንም ነገር ማድረግ ትችላላቹ። ሴት ስለሆናችሁ ብቻ አትችሉም የሚሏችሁን አትስሙ። እኔ ሴት አብራሪ መሆን እንደምትችል ምሳሌ እንደሆንኩ ሁሉ በተለያዩ የሥራ መስኮች ምሳሌ የሚሆኑ ብዙ ሴትች አሉ። የፈለጋችሁትን መሆን ትችላላችሁ፤ ከእናንተ የሚጠበቀው ጠንክሮ መሥራት ብቻ ነው" ስትል የቦይንግ 777 እና 787 ረዳት አብራሪ የሆነችው ሉዋም ጌትነት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግራለች። አብራሪዋ ጨምራም በዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ላይ ተሳታፊ በመሆኗ ደስታ እንደተሰማት ገልፃለች። ሉዋም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዚህ ልዩ ቀን ሴቶች ማድረግ የሚችሉትን ለዓለም እንዲያሳዩ መድረኩን ስላመቻቸቸ ምስጋናዋን ገልጻለች። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን አስመልክቶ ወደ ስድስት ከተሞች ሙሉ በሙሉ በሴቶች ብቻ የሚመራ በረራ እንደሚያደርግ መግለጹ ይታወሳል። በዚህም ከዋና አብራሪዎች እስከ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ድረስ ሁሉም የበረራ ሂደት በሴቶች እንደሚከወን ተገልጿል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክ  ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0