129ኛው የዓድዋ ድል በዓል ሞስኮ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በድምቀት ተከበረ

ሰብስክራይብ
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል ሞስኮ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በድምቀት ተከበረ129ኛው የዓድዋ ድል በዓል "ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል" በሚል መሪ ቃል በሞስኮ እና በአካባቢው የሚገኙ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት በሞስኮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በድምቀት ተከብሯል።በበዓሉ ላይ በሩሲያ ፌድሬሽን የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ገነት ተሾመ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የዓድዋ ድል በዓል የጀግንነት መገለጫ፣ የጥቁር ህዝቦች ኩራት እና በመላው ዓለም የሚገኙ ጥቁር ህዝቦች ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ለመውጣት ተስፋን የሰነቁበት እና መነቃቃትን የፈጠሩበት ታሪካዊ ድል እንደሆነ ተናግረዋል።የዘመኑም ትውልድ ከዚህ የቀድሞ አባቶቻችን የሀገር ፍቅር ስሜትና አርበኝነት መማር እንደሚገባው አስገንዝበዋል ሲል በሞስኮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦   APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0