ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ የ2025 ቀዳሚ እቅድ አዲሱን የልማት ባንክ መቀላቀል እንደሆነ ገለጸች

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ የ2025 ቀዳሚ እቅድ አዲሱን የልማት ባንክ መቀላቀል እንደሆነ ገለጸች ኢትዮጵያ በብራዚል መዲና ብራዚሊያ በተካሄደው የ2025 የመጀመሪያው የብሪክስ ተወካዮች ስብሰባ ላይ ተሳትፋለች። የብሔራዊ ባንክ ገዢና የኢትዮጵያ የብሪክስ ተወካይ ማሞ ምህረቱ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታና የብሪክስ ምክትል ተወካይ አምባሳደር ምስጋኑ ረታ ኢትዮጵያን ወክለው በስብሰባው ላይ ተሳትፈዋል። በስብሰባው ላይ ንግግር ያደረጉት ማሞ ምህረቱ ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስርዓትን ማዕከል ያደረገ የባለብዙ ወገን ግኑኝነት እና የጋራ ደህንነትን ለረዥም ጊዜ ስትደግፍ ቆይታለች ብለዋል። አክለውም የ2025 የኢትዮጵያ ቀዳሚ እቅድ አዲሱን የልማት ባንክ መቀላቀል እንደሆነ አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ የብሪክስ ተወካይ በቡድኑ አባል ሀገራት መካከል የተጠናከረ የኢኮኖሚ ትብብር ሊኖር እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0