የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለውን ግጭት በተመለከተ ድርብ መስፈርት ይከተላል ሲሉ በድርጅቱ የሀገሪቱ ተወካይ ተናገሩ

ሰብስክራይብ
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለውን ግጭት በተመለከተ ድርብ መስፈርት ይከተላል ሲሉ በድርጅቱ የሀገሪቱ ተወካይ ተናገሩ "ለኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ግጭት የተሰጠ ትኩረት አለ፤ ነገር ግን ትኩረቱ በዩክሬን ወይም በጋዛ ውስጥ እንዳየነው አይደለም። በግልፅ መናገር የምችለው ድርብ መስፈርት እንዳለ ነው። ምክንያቱም ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ በማሰባሰብ ረገድ ለዩክሬን፣ ለእስራኤል እንዲሁም ለጋዛ የተሰጠውን ትኩረት ስትመለከቱ፤ ከኮንጎ ጋር የሚወዳደር አይደለም" ሲሉ በተባበሩት መንግሥታት የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ልዑክ ዚኖን ሙኮንጎ ንጌይ ለስፑቲኒክ ተናግረዋል። በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ያለው ሁኔታ እየተባባሰ ቢመጣም፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ግን፤ ሩዋንዳ ከጎረቤት ሀገሯ ግዛት እንድትወጣ የሚጠይቅ ውሳኔ እስካሁን አላሳለፈም ሲሉ ልዑኩ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0