ኡጋንዳ የዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ ኢቱሪ ክልል መዲና በሆነችው ቡኒያ ከተማ ወታደሮቿን አሰማራች

ሰብስክራይብ
ኡጋንዳ የዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ ኢቱሪ ክልል መዲና በሆነችው ቡኒያ ከተማ ወታደሮቿን አሰማራች ስምሪቱ "ሚሊሻዎች ህዝቡ ላይ ጭፍጨፋ" መፈፀማቸውን ተከትሎ የመጣ እንደሆነ የኡጋንዳ ጦር ቃል አቀባይ ገልጿል ሲሉ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የኤም23 አማጺ ቡድን የደቡብ ኪቩ ዋና ከተማ ቡካቩን ባሳለፍነው ሳምንት ተቆጣጥሯል። በኡጋንዳ አቅራቢያ የምትገኘው ቡኒያ በተደጋጋሚ በታጣቂ ቡድኖች ኢላማ ውስጥ እንደምትገባ ነው የተገለጸው። የኡጋንዳ ጦር ኃይል መሪ ሙሁዚ ካይኔሩጋባ፤ "በቡኒያ የሚገኙ ሁሉም ኃይሎች መሳሪያቸውን እንዲያስረክቡ" 24 ሰዓት ሰጥተው ነበር። ይህንን ካላደረጉ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው በኤክስ የትሥሥር ገፃቸው ላይ ባጋሩት መልዕክት አስጠንቅቀዋል። የኡጋንዳ ጦር፤ ተጨማሪ ማብራሪያ ሳይሰጥ ታጣቂ ቡድኖችን ለማስቆም በምስራቃዊ ኮንጎ "መከላከያውን እንደሚያጠናክር" ጥር ወር መገባደጃ ላይ አስታውቋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0