ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥረት ምሳሌ እንደሚሆን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ጠቆሙፕሬዝዳንቱ ይህን ያሉት፤ አዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው የመስኖ ልማትና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ምርታማነትን ትኩረቱ ባደረገው ጉባዔ ላይ ነው። በጉባዔው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ታዬ፤ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አመራር ሰጭነት፤ በአፍሪካ ማህብረሰብ አቀፍ የግብርና ልማት ሽግግርን እየመራች ነው ብለዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብርን ለአብነት ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ 40 ቢሊየን ችግኝ በመትከል የደን ሽፋንን ማሳደግ እንደተቻለ እና በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋገጡ መቻሉን ጠቅሰዋል። የሀገሪቱን የስንዴ ልማት ተነሳሽነት በተመለከተ፤ ከውጭ የሚገባ ስንዴን በማቆም የስንዴ ምርት ፍጆታዋን በራሷ አቅም ማምረት ችላለች ብለዋል። ይህም አፍሪካ ራሷን መመገብ እንደምትችል ማረጋገጫ ነው ሲሉ አስረግጠዋል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥረት ምሳሌ እንደሚሆን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ጠቆሙ
ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥረት ምሳሌ እንደሚሆን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ጠቆሙ
Sputnik አፍሪካ
ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥረት ምሳሌ እንደሚሆን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ጠቆሙፕሬዝዳንቱ ይህን ያሉት፤ አዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው የመስኖ ልማትና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ምርታማነትን... 13.02.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-02-13T15:20+0300
2025-02-13T15:20+0300
2025-02-13T15:44+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2025
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥረት ምሳሌ እንደሚሆን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ጠቆሙ
15:20 13.02.2025 (የተሻሻለ: 15:44 13.02.2025)
ሰብስክራይብ