ሶቪየት ህብረት ናዚን ድል ያደረገችበት 80ኛ ዓመት አስመልክቶ በዛምቢያ የተገነባ የመታሰቢያ ሐውልት ይፋ ሆነ

ሰብስክራይብ
ሶቪየት ህብረት ናዚን ድል ያደረገችበት 80ኛ ዓመት አስመልክቶ በዛምቢያ የተገነባ የመታሰቢያ ሐውልት ይፋ ሆነ ሥነ-ሥርዓቱ ሉሳካ በሚገኘው የሩሲያ ማዕከል ጥር 24 ቀን ተከናውኗል። በዝግጅቱ ላይ በዛምቢያ የሚኖሩ የሩሲያ ዜጎች፣ የሩሲያ ኤምባሲ ሰራተኞች እና በሩሲያ ለመማር ፍላጎት ያላቸው ዛምቢያውያን ወጣቶች ተገኝተዋል። የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ 80ኛው ዓመት የድል ቀን በዓል አከባበር ማስጀመሪያ ነው ሲሉ የሩሲያ አምባሳደር አዚም ያራክሜዶቭ ተናግረዋል። የመታሰቢያ ሐውልቱ ሉሳካ በሚገኘው የሩሲያ ማዕከል አነሳሽነት እንደተገነባ ተገልጿል። ለሩሲያ ዜጎች እና ስለ ሩሲያ ማወቅ ለሚፈልጉ የዛምቢያ ዜጎች የመስህብ ቦታ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። በያዝነው የፈረንጆቹ ዓመት ሶቪየት ህብረት በናዚ ጀርመን ላይ ድል የተቀዳጀችበት 80ኛ ዓመት ይከበራል። በሩሲያ እና በሌሎች በርካታ ሀገራት ውስጥ የዚህ መታሰቢያ አካል የሆኑ በርካታ ዝግጅቶችን ለማከናወን ታቅዷል። በሉሳካ የሩሲያ ማዕከል የተለቀቀ ቪዲዮ በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0