የሩሲያ ዩናይትድ ፓርቲ እና የደቡብ አፍሪካው ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲ ተወካዮች በሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ ኮንግረስ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገቡ

ሰብስክራይብ
    የሩሲያ ዩናይትድ ፓርቲ እና የደቡብ አፍሪካው ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲ ተወካዮች በሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ ኮንግረስ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገቡከብሪክስ አጋር እህት ድርጅቶች አንዱ የሆነውን የሩሲያ ዩናይትድ ፓርቲን ወክለው የተገኙት፤ በሩሲያ ፌድሬሽን ምክር ቤት የዓለም አቀፍ ጉዳዩች ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት  አንድሬይ ክሊሞቭ ናቸው። የደቡብ አፍሪካውን ገዢ ፓርቲ አፍሪካ ናሽናል ኮንግረስን ወክለው በአዲስ አበባ የተገኙት ደግሞ የፓርቲው ማእከላዊ ኮሚቴ አባል ኖክሶሎ ኪቬት ናቸው። ተወካይዋ አዲስ አበባ ሲደርሱ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ከጁቡቲ፣ ናይጀሪያ፣ ዙምባብዌ፣ ታንዛኒያ፣ ኩባ፣ ቱርኪሚንታን እና ካዛኪስታን ገዢ ፓርቲዎች የተወከሉ እንግዶች ምሽቱን አዲስ አበባ ገብተዋል።በዛሬው እለት ጀምሮ በመጪው እሁድ በሚጠናቀቀው የብልፅግና ሁለተኛ ኮንግረንስ ላይ፤ ከጎረቤት ሀገሮች እና ከብሪክስ ህብረት እህት የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ 43  ተወካዩች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ሚዲያዎች ዘግበዋል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0