ሩሲያ ለአንጎላ 50 አምቡላንሶችን ለገሰች በአንጎላ የሩሲያ አምባሳደር ቭላድሚር ታራሮቭ የሩሲያ ሞዴል የሆኑትን ጋዜል ቢዝነስ 4x4 ተሽከርካሪዎች ለሀገሪቱ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሲልቪያ ሉቱኩታ አስረክበዋል። የአምቡላንሶቹ ድጋፍ ሩሲያ ለአንጎላ ሕዝብ የምታደርገው የሰብዓዊ ዕርዳታ አካል እንደሆነ የሩሲያ ኤምባሲ በቴሌግራም ቻናሉ ገልጿል። የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ጃዎ ሎሬንሶ ለሩሲያ አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ባቀረቡት የግል ጥያቄ መሰረት ተሽከርካሪዎቹ ወደ አንጎላ በነፃ እንደተላኩ ታራሮቭ ጠቁመዋል። 685,500 ዶላር የሚጠጋ ወጪ የተደረገበት የሰብዓዊ ፕሮጀክት የሩሲያ መንግሥት በዚህ ዓመት በአፍሪካ አህጉር ካከናወናቸው ትልቅ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ እንደሆነም ተናግረዋል። ከሩሲያ ህዝብ እና መንግሥት የተገኘው ይህ ስጦታ አንጎላውያንን ለረጅም ጊዜ እና በአስተማማኝ ሁኔታ እንደሚያገለግል እና ያስቀረው ወጪ የብሔራዊ ጤና አገልግሎት ስርዓቱን ለማሻሻል ይውላል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
ሩሲያ ለአንጎላ 50 አምቡላንሶችን ለገሰች
ሩሲያ ለአንጎላ 50 አምቡላንሶችን ለገሰች
Sputnik አፍሪካ
ሩሲያ ለአንጎላ 50 አምቡላንሶችን ለገሰች በአንጎላ የሩሲያ አምባሳደር ቭላድሚር ታራሮቭ የሩሲያ ሞዴል የሆኑትን ጋዜል ቢዝነስ 4x4 ተሽከርካሪዎች ለሀገሪቱ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሲልቪያ ሉቱኩታ አስረክበዋል። የአምቡላንሶቹ ድጋፍ ሩሲያ ለአንጎላ ሕዝብ... 11.08.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-08-11T11:02+0300
2024-08-11T11:02+0300
2024-08-11T11:46+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий