የሴኔጋል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዩክሬን በማሊ ቲንዛዎቴን ክልል ለደረሰው የሽብር ጥቃት የሰጠችውን ድጋፍ አወገዙ 9 የሴኔጋል ሲቪል ማህበራት በጋራ ባወጡት መግለጫ "እኛ የሴኔጋል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዩክሬን ለአሸባሪ ቡድኖች የምታደርገውን ድጋፍ እያወገዝን የሴኔጋል ባለስልጣናት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን" ማለታቸውን ስፑትኒክ አፍሪካ ያገኘው የመግለጫው ቅጂ ያሳያል። እ.አ.አ. ሐምሌ 25 አንድ የአሸባሪ ቡድን ክፍል በማሊ ጦር እና የሩሲያ ወታደራዊ አሰልጣኞች ላይ በማሊ ቲንዛዎቴን ክልል ባደረሰው ጥቃት ብዙዎች ተገድለዋል። በምላሹም የማሊ እና የቡርኪናፋሶ መከላከያ ሃይሎች ለጥቃቱ ተጠያቂ በሆኑት ታጣቂዎች ላይ ተከታታይ የአየር ጥቃት በማድረስ አንድ ከፍተኛ የሽብር መሪን ጨምሮ በርካቶችን ገድለዋል። ፈራሚዎቹ እንዳሉት፦ ኪዬቭ አሸባሪ ቡድኖችን ትደግፋለች በማለት የዩክሬን የስለላ ድርጅት ቃል አቀባይ አንድሬ ዩሶቭ የሰጡት መግለጫ በኢንተርኔት ተሰራጭቷል። በሴኔጋል የሚገኘው የዩክሬን ኤምባሲ በማህበራዊ ሚዲያ ባሰራጨው ቪዲዮ ዩሶቭ "በእዚህ ግጭት አውድ ዩክሬን አማፂያኑን ትደግፋለች" ሲል ተናግሯል። "በዳካር የሚገኘው የዩክሬን ዲፕሎማሲ በማሊ ግዛትም ሆነ በማንኛውም የአፍሪካ መንግሥት ላይ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ማካሄዱ ተገቢ አይደለም" ሲል መግለጫው አትቷል። ድርጅቶቹ “በምዕራቡ ዓለም የገንዘብ ድጋፍ በሚደረግላቸው እና በሚሰለጠኑ አሸባሪ ቡድኖች” በተካሄደው ጥቃት አውድ የሳህል ቀጠና “አስጊ” የፀጥታ ሁኔታን አውግዘው ለማሊ ጦር እና ለሳህል ሀገራት ጥምረት የመከላከያ ኃይሎች ድጋፋቸውን ገልጸዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
https://amh.sputniknews.africa
የሴኔጋል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዩክሬን በማሊ ቲንዛዎቴን ክልል ለደረሰው የሽብር ጥቃት የሰጠችውን ድጋፍ አወገዙ
የሴኔጋል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዩክሬን በማሊ ቲንዛዎቴን ክልል ለደረሰው የሽብር ጥቃት የሰጠችውን ድጋፍ አወገዙ
Sputnik አፍሪካ
የሴኔጋል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዩክሬን በማሊ ቲንዛዎቴን ክልል ለደረሰው የሽብር ጥቃት የሰጠችውን ድጋፍ አወገዙ 9 የሴኔጋል ሲቪል ማህበራት በጋራ ባወጡት መግለጫ "እኛ የሴኔጋል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዩክሬን ለአሸባሪ ቡድኖች የምታደርገውን... 03.08.2024, Sputnik አፍሪካ
2024-08-03T16:35+0300
2024-08-03T16:35+0300
2024-08-03T17:23+0300
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/i/logo/logo-social.png
африка общий
2024
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
африка общий
африка общий
የሴኔጋል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዩክሬን በማሊ ቲንዛዎቴን ክልል ለደረሰው የሽብር ጥቃት የሰጠችውን ድጋፍ አወገዙ
16:35 03.08.2024 (የተሻሻለ: 17:23 03.08.2024)
ሰብስክራይብ