ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች ሀገሪቱ ተረጂነቷን ሙሉ በሙሉ ልታስወግድ እንደምትችል ያስመሰከረ ነው ሲሉ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች ሀገሪቱ ተረጂነቷን ሙሉ በሙሉ ልታስወግድ እንደምትችል ያስመሰከረ ነው ሲሉ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ተናገሩ ንግግሩን ያደረጉት “ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር፣ ነጻነት እና ሉዓላዊነት” በሚል መሪ ሐሳብ በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ ነው። አለሙ ስሜ በግብርና በተለይም በደረቃማ ወራት መስኖን በመጠቀም ስንዴን ማምረት መቻሉን እንዲሁም በኢንዱስትሪው ዘርፍ የታዩ እድገቶችን አንስተዋል። ሀገሪቱ ያላትን የተፈጥሮ ሀብት በአግባቡ ተጠቅማ ተረጂነትን ለመቀነስ የያዘችውን ግብ ለማሳካት የሀገሪቱ አመራሮች ቆራጥ እርምጃ ሊወስዱ ይገባል ሲሉም አፅንኦት ሰጥተዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
አዳዲስ ዜናዎች
0